Telegram Group & Telegram Channel
የእኔ ታሪክ (በ አዲስ ምዕራፍ)
ቪቪያን እንደፃፈችው........

የሰው ልጅ ታሪክ መጨረሻ የለውም። ሞት መጨረሻ ነው ብዬ እንዳልደመደም ከሚያደርጉኝ ነገሮች አንዱ ልጅ ነው። የአባቴ ታሪክ እዚህ ላይ ያበቃ ቢመስልም በእኔ እና በአሌፍ ግን ነፍስ ዘርቶ ቀጥሏል። እንዲህ ሆነ.........ወደኋላ ተመልሳ ከአባቷ ጋ ያሳለፈችውን የመጨረሻ ቀን አስታወሰች።


ያቀፏት የሕዝቅኤል እጆች ድንገት ተንሸራተው ሲወድቁ የእርሷም ልብ ላይ የሆነ ነገር ቁርጥ ብሎ ሲወድቅ ታወቃት። ለመናገር ቃላቶች አልነበሯትም አይኗ ብቻ በሚያፈሰው ውሃ ያወራል። ያ ሕይወቱን ሙሉ በመከራ ያሳለፈው ሕዝቅኤል ለዘለዓለም አልተነሳም። ከቁስሉ ሊያገግም ፣ ለብዙ አመት የተከደነው ጥርሱ ሊስቅ ፣ በእንባ ብዛት የሟሙ አይኖቹ እንደገና የተስፋ ጭላንጭል ሊያበሩ በነበረበት ቅፅበት ሕዝቅኤል ድንገት አመለጠ። ከእነሱ ከእናት እና አባቱ፣ ከእህቱ እና ከወንድሙ ጋ ተቀላቀለ....... ህይወት ፍትሃዊ አይደለችም። ያንን ሁሉ የስቃይ እና የመከራ አመታት ሲያሳልፍ ዞር ብሎ ያላየው ሞት...... ለደስታው በተቃረበ ሰዓት ግን ሊወስደው አሰፈሰፈ።


ማቲያስ የተደወለለትን ስልክ አናግሮ ከጨረሰ በኋላ አንድ ጋዜጣ እያነበበ የነበረ ሰው አጠገብ ሄዶ ተቀመጠ። የሰውዬውን ሁኔታ ከላይ እስከታች አጤነው....የሚያውቀው መስሎ ተሰማው ግን የት እንደሆነ ማስታወስ አልቻለም ለዛም ሊያናግረው ፈልጎ ጉሮሮውን ጠራረገ። እንዴት ዋሉ አባ.....? ሰውየው ጋዜጣቸውን ዝቅ አድርገው ወደጠራቸው ሰው ዞር አሉና ፈገግ አሉ። ምኔን አይተህ ነው አባ ያልከኝ ልጄ .......ፂምወትን አለ ቀለል ያሉ ሰው እንደሆኑ ከንግግራቸው ተረድቶ......ቀጠል አድርጎም እርሶስ ምኔን አይተው ነው ልጄ ያሉኝ አለ ጨዋታ ለመፍጠር ያክል.......እሳቸውም ወጣትነትን ብለው ፈገግ አሉ። ማቲያስ እባላለሁ አለ እጁን ለሰላምታ እየዘረጋላቸው፤ ሰውየው ድንግጥ ብለው ማቲያስ አሉ የተዘረጋላቸውን እጅ እየጨበጡ። አወ የእርሶስ አለ ማቲያስ የፊታቸውን መቀየር እያጤነ። የእኔን ስም ነበር ማቲያስ ያልኩህ ማቲያስ እባላለሁ ..........የስማችን መመሳሰል ገርሞኝ ነውኮ መደንገጤ።


ወጣቱ ማቲያስ ወዲያው የሜሮን የቀድሞ ፍቅረኛ አእምሮው ላይ ብልጭ አለ። ጋሽ ሕዝቅኤል ጓደኛወት ነው? አብርሃምም?.....ሽማግሌው ደነገጠ ማነህ አንተ?..............መጀመሪያ ጥያቄዬን ይመልሱልኛ.... አወ ማን ነህ?......የሜሮን ልጅ.........በእድሜ ብዛት የማያረጀወሰ የሽማግሌው ማትያስ ፍቅር ስሟን ሲሰማ እንደገና አገረሸ። ወጣቱን አስተዋለው እውነትም እሷን ይመስላል ..........እኔኮ አመጣጤ ሕዝቅኤል መታመሙን ሰምቼ ነበር......አለ አሁንም ድንጋጤው እንደወረረው። ና ወደውስጥ ጋሽ ሕዝቅኤልንም እየው እማዬም አለች.........ተያይዘው ወደውስጥ ገቡ።.......ሲገቡ ግን የሕዝቅኤል አይኖች ከሚወደው ጓደኛው ከማትያስም በቅፅበታት ቀድመው ተከድነዋል።


ሆስፒታሉ ሌላ ድባብ ሞልቶታል ቃል የሞላው ቃል አልባ እንባ ከየ አቅጣጫው ይፈሳል ማቲያስ በቁሙ ራደ። ሀዘን ሀዘን ብቻ ተነበበ። ሁሉም የምሬት እንባውን ያነባል......የአሌፍ ግን ቃልም አለው። ለዚህ ነው እንዳውቅህ ያደረግከው? ትተኸኝ ለመሄድ...አባ ለምን? እስከዛሬ ትናፍቀኝ አልነበረ? ስታገኘኝ ጥለኸኝ ለመሔድ ነበር?


ግን ሆነ ሕዝቅኤል ላይመለስ አይኖቹ ተከደኑ። የሚወዱትም ነፍሶች ላይጠገኑ ተሰበሩ። ስርዓተ ቀብሩም ራቢያም ራሷ በተገኘችበት ተፈፀመ።ራቢያ ለዚህ ሁሉ አመታት አፍና የያዘችውን የስቃይ እንባ በመቃብሩ ላይ ዘረገፈችው አልቅሳ አልቅሳ አልጠገበችም አትጠግብምም። አለመኖሩን ሳታይ አምና የነበረችው ራቢያ አይታ ስታረጋግጥ ግን ለመቀበል አልቻለችም አቃታት።


ኤልሳ ልትናገር ይቅርና መቆም አቅቷት ለቀብሩም በሰወች ተደግፋ ነበር የመጣችው። የመጨረሻ ቃሏ " ላልድን ሰበርከኝ አይደል?" የሚል ነበር ከዛ ቃል በኋላ ከ አፏ የወጣ አንድም ቃል የለም። የእሷም አንደበት ከ ህዝቅኤል ጋር ተቀበረ።


ቪቪያን ውስጧ ነው የሚያወራው አይኗ ደግሞ በእንባ ቃላቶቹን ያወጣል። ብቻ ግን ስትታይ ከማዘን አልፎ ሕመሟ ይጋባል ።
ጓደኛው ማቲያስ ቪቪያንን አይቷት ውስጧን አነበበው። እንደ ሕዝቅኤልም ሊጠብቃት ለራሱ ቃል ገባ።
ሁሉንም ሰው በአንድ ላይ የሰበረ ቀን.....

ይቀጥላል ........

@nibab_lehiwot
@nibab_lehiwot
@nibab_lehiwot



tg-me.com/nibab_lehiwot/196
Create:
Last Update:

የእኔ ታሪክ (በ አዲስ ምዕራፍ)
ቪቪያን እንደፃፈችው........

የሰው ልጅ ታሪክ መጨረሻ የለውም። ሞት መጨረሻ ነው ብዬ እንዳልደመደም ከሚያደርጉኝ ነገሮች አንዱ ልጅ ነው። የአባቴ ታሪክ እዚህ ላይ ያበቃ ቢመስልም በእኔ እና በአሌፍ ግን ነፍስ ዘርቶ ቀጥሏል። እንዲህ ሆነ.........ወደኋላ ተመልሳ ከአባቷ ጋ ያሳለፈችውን የመጨረሻ ቀን አስታወሰች።


ያቀፏት የሕዝቅኤል እጆች ድንገት ተንሸራተው ሲወድቁ የእርሷም ልብ ላይ የሆነ ነገር ቁርጥ ብሎ ሲወድቅ ታወቃት። ለመናገር ቃላቶች አልነበሯትም አይኗ ብቻ በሚያፈሰው ውሃ ያወራል። ያ ሕይወቱን ሙሉ በመከራ ያሳለፈው ሕዝቅኤል ለዘለዓለም አልተነሳም። ከቁስሉ ሊያገግም ፣ ለብዙ አመት የተከደነው ጥርሱ ሊስቅ ፣ በእንባ ብዛት የሟሙ አይኖቹ እንደገና የተስፋ ጭላንጭል ሊያበሩ በነበረበት ቅፅበት ሕዝቅኤል ድንገት አመለጠ። ከእነሱ ከእናት እና አባቱ፣ ከእህቱ እና ከወንድሙ ጋ ተቀላቀለ....... ህይወት ፍትሃዊ አይደለችም። ያንን ሁሉ የስቃይ እና የመከራ አመታት ሲያሳልፍ ዞር ብሎ ያላየው ሞት...... ለደስታው በተቃረበ ሰዓት ግን ሊወስደው አሰፈሰፈ።


ማቲያስ የተደወለለትን ስልክ አናግሮ ከጨረሰ በኋላ አንድ ጋዜጣ እያነበበ የነበረ ሰው አጠገብ ሄዶ ተቀመጠ። የሰውዬውን ሁኔታ ከላይ እስከታች አጤነው....የሚያውቀው መስሎ ተሰማው ግን የት እንደሆነ ማስታወስ አልቻለም ለዛም ሊያናግረው ፈልጎ ጉሮሮውን ጠራረገ። እንዴት ዋሉ አባ.....? ሰውየው ጋዜጣቸውን ዝቅ አድርገው ወደጠራቸው ሰው ዞር አሉና ፈገግ አሉ። ምኔን አይተህ ነው አባ ያልከኝ ልጄ .......ፂምወትን አለ ቀለል ያሉ ሰው እንደሆኑ ከንግግራቸው ተረድቶ......ቀጠል አድርጎም እርሶስ ምኔን አይተው ነው ልጄ ያሉኝ አለ ጨዋታ ለመፍጠር ያክል.......እሳቸውም ወጣትነትን ብለው ፈገግ አሉ። ማቲያስ እባላለሁ አለ እጁን ለሰላምታ እየዘረጋላቸው፤ ሰውየው ድንግጥ ብለው ማቲያስ አሉ የተዘረጋላቸውን እጅ እየጨበጡ። አወ የእርሶስ አለ ማቲያስ የፊታቸውን መቀየር እያጤነ። የእኔን ስም ነበር ማቲያስ ያልኩህ ማቲያስ እባላለሁ ..........የስማችን መመሳሰል ገርሞኝ ነውኮ መደንገጤ።


ወጣቱ ማቲያስ ወዲያው የሜሮን የቀድሞ ፍቅረኛ አእምሮው ላይ ብልጭ አለ። ጋሽ ሕዝቅኤል ጓደኛወት ነው? አብርሃምም?.....ሽማግሌው ደነገጠ ማነህ አንተ?..............መጀመሪያ ጥያቄዬን ይመልሱልኛ.... አወ ማን ነህ?......የሜሮን ልጅ.........በእድሜ ብዛት የማያረጀወሰ የሽማግሌው ማትያስ ፍቅር ስሟን ሲሰማ እንደገና አገረሸ። ወጣቱን አስተዋለው እውነትም እሷን ይመስላል ..........እኔኮ አመጣጤ ሕዝቅኤል መታመሙን ሰምቼ ነበር......አለ አሁንም ድንጋጤው እንደወረረው። ና ወደውስጥ ጋሽ ሕዝቅኤልንም እየው እማዬም አለች.........ተያይዘው ወደውስጥ ገቡ።.......ሲገቡ ግን የሕዝቅኤል አይኖች ከሚወደው ጓደኛው ከማትያስም በቅፅበታት ቀድመው ተከድነዋል።


ሆስፒታሉ ሌላ ድባብ ሞልቶታል ቃል የሞላው ቃል አልባ እንባ ከየ አቅጣጫው ይፈሳል ማቲያስ በቁሙ ራደ። ሀዘን ሀዘን ብቻ ተነበበ። ሁሉም የምሬት እንባውን ያነባል......የአሌፍ ግን ቃልም አለው። ለዚህ ነው እንዳውቅህ ያደረግከው? ትተኸኝ ለመሄድ...አባ ለምን? እስከዛሬ ትናፍቀኝ አልነበረ? ስታገኘኝ ጥለኸኝ ለመሔድ ነበር?


ግን ሆነ ሕዝቅኤል ላይመለስ አይኖቹ ተከደኑ። የሚወዱትም ነፍሶች ላይጠገኑ ተሰበሩ። ስርዓተ ቀብሩም ራቢያም ራሷ በተገኘችበት ተፈፀመ።ራቢያ ለዚህ ሁሉ አመታት አፍና የያዘችውን የስቃይ እንባ በመቃብሩ ላይ ዘረገፈችው አልቅሳ አልቅሳ አልጠገበችም አትጠግብምም። አለመኖሩን ሳታይ አምና የነበረችው ራቢያ አይታ ስታረጋግጥ ግን ለመቀበል አልቻለችም አቃታት።


ኤልሳ ልትናገር ይቅርና መቆም አቅቷት ለቀብሩም በሰወች ተደግፋ ነበር የመጣችው። የመጨረሻ ቃሏ " ላልድን ሰበርከኝ አይደል?" የሚል ነበር ከዛ ቃል በኋላ ከ አፏ የወጣ አንድም ቃል የለም። የእሷም አንደበት ከ ህዝቅኤል ጋር ተቀበረ።


ቪቪያን ውስጧ ነው የሚያወራው አይኗ ደግሞ በእንባ ቃላቶቹን ያወጣል። ብቻ ግን ስትታይ ከማዘን አልፎ ሕመሟ ይጋባል ።
ጓደኛው ማቲያስ ቪቪያንን አይቷት ውስጧን አነበበው። እንደ ሕዝቅኤልም ሊጠብቃት ለራሱ ቃል ገባ።
ሁሉንም ሰው በአንድ ላይ የሰበረ ቀን.....

ይቀጥላል ........

@nibab_lehiwot
@nibab_lehiwot
@nibab_lehiwot

BY ሕይወትን - በገፅ


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 283

Share with your friend now:
tg-me.com/nibab_lehiwot/196

View MORE
Open in Telegram


ሕይወትን በገፅ Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

A Telegram spokesman declined to comment on the bond issue or the amount of the debt the company has due. The spokesman said Telegram’s equipment and bandwidth costs are growing because it has consistently posted more than 40% year-to-year growth in users.

Find Channels On Telegram?

Telegram is an aspiring new messaging app that’s taking the world by storm. The app is free, fast, and claims to be one of the safest messengers around. It allows people to connect easily, without any boundaries.You can use channels on Telegram, which are similar to Facebook pages. If you’re wondering how to find channels on Telegram, you’re in the right place. Keep reading and you’ll find out how. Also, you’ll learn more about channels, creating channels yourself, and the difference between private and public Telegram channels.

ሕይወትን በገፅ from ms


Telegram ሕይወትን - በገፅ
FROM USA